“የቀረበብኝ ክስ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን የሚጋፋ ነው” መስከረም አበራ
ከሦስት ሳምንታት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ በዋስ የተለቀቀችው የ“ኢትዮ ንቃት” የማኅበራዊ ሚዲያ መስራች እና ባለቤት መስከረም አበራ የቀረበባት ክስ ሃሳብን በነጻነት...
በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጥቁር በመልበሳቸው ምክንያት አገልግሎት ተነፈጉ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተከሰተውን ችግር ተከትሎ ሰኞ ጥር 29/2015 ዓ.ም. ከተጀመረው የነነዌ ጾም ጋር ምዕመናን ጥቁር...
የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ
የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ የቀድሞ የወላይታ ዞን አመራሮች የነበሩ ግለሰቦችን ጨምሮ 20 ተጠርጣሪዎች በወላይታ ሶዶ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ...
ፓለቲከኛ አብረሃ ደስታ ታሰሩ
ፍርድ ቤት የቀረቡት የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣን አቶ አብርሐ ደስታ “ግጭት በመቀስቀስ” እና “ሕገ-ወጥ ሽጉጥ ይዞ በመገኘት” መጠርጠራቸውን ጠበቃቸው ተናገሩ። አቶ...
በአዲስ አበባ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 625 ደረሰ
በአዲስ አበባ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 625 ደረሰ። በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 625 መድረሱን የአዲስ...
የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር መነጋገራቸው ተገለጸ
በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ መንግሥት ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ማይክ ሐመር በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር...
ሁለት እስረኞች በድብደባ ህይወታቸው እንዳለፈ የአይን እማኞች ለፍርድ ቤት ገለፁ
“ፊቴ ላይ ነው ልቡን ረግጠው የገደሉት፣ የእስር ቤቱ ኃላፊ እያለ ነው የተደበደብነው”
“ሁላችንም ዋስትና የለንም። በሚቀጥለው የእኔን የሞት ዜና ልትሰሙ ትችላላችሁ”
“ሳትፈርዱብን ገድለው ይጨርሱናል” 1ኛ ተከሳሽ...
ኦህዴድ በዞንና በከተማ አስተዳደሮች አዳዲስ የአመራር ምደባ አደረገ
በጨፌ ኦሮሚያ አብላጫ ወንበር በመያዝ የኦሮሚያ ክልልን በመምራት ላይ የሚገው የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) በዞን እና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ አዳዲስ የአመራር ምደባ ማድረጉን...
የፖሊስ ኃይል በዜጎች ላይ ከፍተኛ ጥቃት ከሚፈጽምባቸው ሀገራት ኢትዮጵያ አንዷ ሆና ተፈረጀች
በዓለም ላይ በፖሊስ አማካይነት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከሚፈጸምባቸው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ ተገለጸ፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ ምርምር ሲያደርግ የሰነበተው አንድ ዓለም ዓቀፍ ተቋም፣ በ2016...
ገደቡ ካልተነሳ የበጀት ድጎማውን እንደማይለቅ የአውሮፓ ህብረት አስታወቀ
የአውሮፓ ኅብረት የሰብዓዊ ዕርዳታ የሚያቀርቡ ድርጅቶች በትግራይ ክልል ያለ ገደብ እንዲንቀሳቀሱ እስካልተፈቀደ ድረስ፣ ለኢትዮጵያ ያፀደቀው የበጀት ድጎማ እንደማይለቀቅ አስታወቀ።
የኅብረቱ ምክትል ኮሚሽነርና የውጭ ጉዳይና ደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፍ ቦሬል በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ቀውስ መባባስ የአውሮፓ ኅብረትን በእጅጉ እንደሚያሳስበው፣ በዚህ ጉዳይ ላይም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በስልክ መወያየታቸውን ገልጸዋል።
በውይይታቸው ወቅትም በትግራይ ክልል ያለው ሰብዓዊ ቀውስ ኅብረቱን እንደሚያሳስበው ለአቶ ደመቀ እንደገለጹላቸው የጠቆሙት ኃላፊው፣ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅራቢ ድርጅቶች በትግራይ ክልል ያለ ምንም ገደብ እንዲንቀሳቀሱ ሊፈቀድ እንደሚገባ ማሳሰባቸውን ዓርብ ጥር 7 ቀን 2013 ዓ.ም. አስታውቀዋል።
‹‹ይህ የአውሮፓ ኅብረት ጥያቄ አይደለም፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ሕግ የተደነገገ የመንግሥታት ግዴታ ነው፤›› ሲሉም በትዊተር ገጻቸው አመልክተዋል።













