በትግራይ ኤርትራውያን ስደተኞች አደጋ ላይ ናቸው – ተመድ

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ድርጅት በትግራይ ውስጥ እየተባባሰ ባለው ጦርነት መካከል የሚገኙ ወደ 24ሺ የሚሆኑ የኤርትራውያን ስደተኞች ትልቅ አደጋ ላይ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

ማይጸብሪ አካባቢ እየተካሄደ ያለው ውጊያ እየተጠናከረ በመምጣቱ በማይ አኒ እና አዲ ኻሩሽ በተባሉ የመጠለያ ካምፖች ውስጥ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ስደተኞች ደህንነት አደጋ ላይ ናቸው፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ድርጅት እኤአ ከሀምሌ 14 ጀምሮ ወደ መጠለያ ጣቢያዎች ዘንድም ለመድረስ አለመቻሉን ገልጿል፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ስደተኞች ያሉበት ሁኔታ እጅግ እየከፋ መመጣቱንም አስታውቋል፡፡

የ UNHCR ቃለ አቀባይ ባርባራ ባሎች እንደሚሉ ታጣቂ ኃይሎች ወደ ካምፑ ውስጥ ዘልቀው ገብተዋል፡፡ እሳቸው እንደሚሉት ኤርትራውያኑ ስደተኞች በማቋርጥ ፍርሃት ውስጥ ናቸው፡፡ እርዳታዎችን እንዳያገኙ የተቆረጡ ሲሆን ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎችም እየደረሱባቸው እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

ከማይ አኒ ካምፕ ውስጥ ቢያንስ አንድ ስደተኛ ካምፕ ውስጥ ባለ አንድ ታጣቂ መገደሉን የሚገልጽ አስደንጋጭ ዜና ከታመነ ምንጭ ሰምተናል፡፡ ሀምሌ 14 ከተገደለው አንድ ሰደተኛ ሞት በኋላ ይህኸኛው ተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡