የህወኃት አመራሮች እየፈጸሙት ያለው ህገ-ወጥ ድርጊት ካላቸውን ረጅም የፖለቲካ ልምድ አኳያ ተገቢ አለመሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
–
ለትግራይ ህዝብ ክብርና ጥቅም ሲባል የፌዴራል መንግስትና የህወኃት አመራሮች በድርድር ችግራቸውን ሊፈቱ ይገባልም ነው ያሉት።
–
በኢፌዴሪ ህገ- መንግስት አንቀፅ 102 ንኡስ ቁጥር 1 መሰረት በፌዴራልም ሆነ በክልሎች የሚደረጉ ምርጫዎችን የማስፈፀም ስልጣን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መሆኑ በግልጽ ተቀምጧል።
–
በኢትዮጵያ ወረርሽኙ መከሰቱ እንደታወቀ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከሚመለከታቸው ባለደርሻ አካላት ጋር በመካከር ቦርዱ ቀደም ሲል ባወጣው የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ማካሄድ የማይችል መሆኑን አሳውቋል።
–
ይሁንና በትግራይ ክልል ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና ውጭ ጳጉሜን 4 ቀን 2012 ዓ.ም ክልላዊ ምርጫ ተካሂዷል።
ምርጫው የትግራይ ክልልን እያስተዳደረ ያለው የህወኃት አመራሮች ህገ ወጥ ድርጊት መሆኑን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናግረዋል።
–
የህወኃት አመራሮች እየፈጸሙት ያለው ህገ-ወጥ ድርጊት ካላቸው የረጅም ጊዜ የፖለቲካ ልምድ አኳያ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል።